ኢትዮጵያ!ታላቅ ሕዝብ እና ታላቅ ሐገር!
1 ከ እስራኤላውያን ውጪ ያለ ታላቅ ህዝብ ፡-ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያዊው ዝሪ አንድ ሚልዮን ሰራዊትና ሶስት መቶ ሰረገሎችን ይዞ ወደ እስራኤል ዘመተ በዚህም የተደናገጠው የእስራኤል ንጉስ ወደ ፈጣሪው ጽሎት አደረሰ ጸሎትም ሲያደርስ ኢትዮጵያውያኑን " ታላቅ ሕዝብ " በማለት ጠራቸው እንግሊዘኛው መጽሀፍ ቅዱስ ይሄንን ሲተርጉመው " The Great Ethiopians " The Great Nation " በማለት ነው፡፡
“ኢትዮጵያዊውም ዝሪ አንድ ሚሊዮን ሰዎችና ሦስት መቶ ሰረገሎች ይዞ ወጣባቸው ወደ መሪሳም መጣ። አሳም ሊጋጠመው ወጣ፥ በመሪሳም አጠገብ ባለው በጽፋታ ሸለቆ ውስጥ ተሰለፉ። አሳም። አቤቱ፥ በብዙም ሆነ በጥቂቱ ማዳን አይሳንህም አቤቱ አምላካችን ሆይ፥ በአንተ ታምነናልና፥ በስምህም በዚህ ታላቅ ሕዝብ ላይ መጥተናልና እርዳን አቤቱ፥ አምላካችን አንተ ነህ ሰውም አያሸንፍህ ብሎ ወደ አምላኩ ወደ እግዚአብሔር ጮኸ።" (2መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 14:9 -11)
ታላቅ ሕዝብ የሚለውን ያዙልኝ
2.የሙሴ በኢትዮጵያ ላይ መሾም
የአይሁድ ፣ የክርስትናና የታሪክ ሊቃውንት ደግሞ በሙሴና በኢትዮጵያ ጉዳይ የሚደንቅ ታሪክ አላቸው:: አይሁዶች "ሙሴ ኢትዮጵያ ሄዶ ኢትዮጵያን አርባ አመት ገዝቷል" ብለው ሲከራክሩ የክርስትናና የታሪክ ሰዎች ደግሞ " ኢትዮጵያ ላይ እግዚአብሔር ሊሾመው ነበር እንጂ የኢትዮጵያ ንጉስ አልነበረም " ይላሉ።
የክርስትና ሊቃውንት የሚጠቅሱት አንዱ መከራክርያ ይሄ ነው። ሙሴ ሲና ተራራ ላይ በቆየ ወቅት እስራኤል የጥጃ ጣኦት አቁመው ለጥጃው መስገድ ጀመሩ:: እግዚአብሔርም በዚህ በጣም ተቆጣ:: ሕዝቡንም ሊያጠፋው እንደወደደና ሙሴንም ለሌላ ታላቅ ሕዝብ መሪ እንደሚያደርገው ገለጸለት ። ይሔ ከእስራኤል ውጭ ያለ ሌላ ታላቅ ሕዝብ ማን ነበር?
“እግዚአብሔርም ሙሴን፦ ከግብፅ ምድር ያወጣኸው ሕዝብህ ኃጢአት ሠርተዋልና ሂድ፥ ውረድ። ካዘዝኋቸው መንገድ ፈጥነው ፈቀቅ አሉ ቀልጦ የተሠራ የጥጃ ምስል ለራሳቸው አደረጉ፥ ሰገዱለትም፥ ሠዉለትም። እስራኤል ሆይ፥ እነዚህ ከግብፅ ምድር ያወጡህ አማልክትህ ናቸው አሉ ፤ሲል ተናገረው እግዚአብሔርም ሙሴን፦ እኔ ይህን ሕዝብ አየሁት፥ እነሆም አንገተ ደንዳና ሕዝብ ነው።አሁንም ቍጣዬ እንዲቃጠልባቸው እንዳጠፋቸውም ተወኝ አንተንም ለታላቅ ሕዝብ አደርግሃለሁ አለው።” (ዘጸአት 32 ፡7-10)
ይሔ ከእስራኤል ጋር የሚወዳደር ሌላ ታላቅ ሕዝብ ማን እደሆነ ጻድቅ የነበረው የእስራኤል ንጉስ ቀድሞ ተናግሮታል(2መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 14:9):: በዘመነ ብሉይ የነበረው ነብዩ አሞጽም የተናገረው ይጠቀሳል ። "የእስራኤል ልጆች ሆይ፥ እናንተ ለእኔ እንደ ኢትዮጵያውያን ልጆቼ አይደላችሁምን?”(ትንቢተ አሞጽ 9፣7 )
ስለዚህ ሙሴ ሊሾምበት የነበረው ታላቅ ሕዝብ ኢትዮጵያ እንደነበረች ጥርጥር የለውም::
የሚደንቀው ግን የእስራኤላውያኑ እይታ ነው። የእስራኤላውያን የቀደሙ የታሪክ ሊቆቻቸውን ዜና መዋእል በመጥቀስ " ሙሴ ኢትዮጵያን አርባ አመት ገዝቷታል" ይሉናል። ይህንንም የጂውሽ ኢንሳይክሎፒዲያ (The Jewish Encyclopedia: A Descriptive Record of the History ..., Volume 9, page 48 edited by Isidore Singer, Cyrus Adle)ተጽፎ እናገኘዋለን፡፡
3. የመጀመርያዋ የእስራኤል ቀዳማዊ እመቤት የሙሴ ሚስት ኢትዮጵይዊቷ ሲፓራ ነበረች።
ኢትዮጵያን አትንኩ !!!
ከመጽሀፍ ቅዱስ እንደምንረዳው ሙሴ በምድር ሁሉ ካሉት ሰዎች " እጅግ ትሁት " እንደነበረና ( ዘኁ 12:3) በምድር ካሉ ሰዎች ሁሉ እግዚአብሔር አፍ ለአፍ እንደሚናገረውና የእግዚአብሔርንም መልክ ያየ ብቸኛው ጻድቅ እንደነበረ በሚገባ ተገልጿል።( ዘኁ 12:8) ታድያ ይህ ቀረህ የማይባለው ጻድቅና የሕግ መምህር ሙሴ መርጦ ያገባት ኢትዮጵያዊቱ ሲፓራን ነው።
በዚህም እስራኤላዊያኑ በማያገባቸው ነገር ገብተው ተናደዱ።ሊቀ ካህናቱ አሮንና ማርያም በይፋ ቁጣቸውን ገለጹ። ግን ምን ያደርጋል:: ሙሴ እንዴት ኢትዮጵያዊቷን ያገባል ብላ ያንጎራጎረችው ማርያም ስለዚህ ድፍረቷ በለምጽ ተቀጣች። ኢትዮጵያን አትንኩ !!!
"ሙሴም ኢትዮጵያይቱን አግብቶአልና ባገባት በኢትዮጵያይቱ ምክንያት ማርያምና አሮን በእርሱ ላይ ተናገሩ። እግዚአብሔርም ተቈጥቶባቸው ሄደ።ደመናውም ከድንኳኑ ተነሣ እነሆም፥ ማርያም ለምጻም ሆነች፥ እንደ አመዳይም ነጭ ሆነች አሮንም ማርያምን ተመለከተ፥ እነሆም፥ ለምጻም ሆና ነበር። አሮንም ሙሴን፦ ጌታዬ ሆይ፥ ስንፍና አድርገናልና፥ በድለንማልና እባክህ፥ ኃጢአት አታድርግብን።" (ኦሪት ዘኍልቍ 12: 1-12)
4. የኢትዮጵያዊቷ ሲፓራ ልጆች
ሙሴ ከኢትዮጵያዊት ሚስቱ ሁለት ልጆችን ወለደ:: እነዚህም ልጆች ስማቸው ጌርሳምና አልዓዛር ነበሩ::
“በዚያን ጊዜ የሙሴ አማት ዮቶር መልሶአት የነበረውን የሙሴን ሚስት ሲፓራን ሁለቱንም ልጆቿን ወሰደ።”(ዘጸ 18:2 )
እነዚህ ልጆች ሲያድጉ ባለስልጣን ሆነው ተሾሙ:: ቁጥራቸውም ታቦተ ጽዮንን ከሚያገለግሉት ከነገደ ሌዊ ሆነ::
"የእግዚአብሔርም ሰው የሙሴ ልጆች በሌዊ ነገድ ተቈጠሩ።የሙሴ ልጆች ጌርሳምና አልዓዛር ነበሩ።የሙሴ ልጅ የጌርሳም ልጅ ሱባኤል በቤተ መዛግብት ላይ ተሾሞ ነበር።"
ከነገደ ሴምና ከኢትዮጵያውያን ተወልደው በ እስራኤል ላይ ባለስልጣን የሆኑ የመጀመርያ ነጭና ጥቁሮች ( መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 23:14-16)
5. እስራኤልን ከግብጽ ወደ ኢየሩሳሌም እየመራ የወሰዳቸው ኢትዮጵያዊው ኦባብ
ሙሴ እስራኤልን ባሕር ከፍሎ ያሻገረ ታላቅ ነብይ ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ግን ሌላ የሚገርም ታሪክ ተጽፏል። ባሕረ ኤርትራን ከፍሎ ያሻገረው ታላቁ ነብይ ወደ ኢየሩሳሌም ሕዝቡን ይዞ የሚሄድበት መንገድ ጠፋው። ምንም እንኳን ቀን በአምደ ደመና ሌት ደግሞ በአምደ ብርሃን እየተመራ ሕዝቡን ይዞ ቢጓዝም ለሙሴ ሌላ ሰው መንገዱን ያሳያው ዘንድ ግድ ነበር። ይሄውም ሰው ኢትዮጵያዊው ኦባብ ራጉኤል ይባላል:: ሙሴ በራሱ አንደበት እንተ ለኛ ለእስራኤላውያን " አይኖቻችን ነህ " ብሎ የመሰከረለትና ሕዝበ እስራኤልን ይዞ ኢየሩሳሌም ያገባቸው ፣ ታቦተ ጽዮንንም ማደርያዋን ያዘጋጅ የነበረ ሃያል ኢትዮጵያዊ :: የኢትዮጵያዊቷ የሙሴ ሚስት ወንድም ኦባብ ወልደ ራጉኤል
"ሙሴም የሚስቱን አባት የምድያማዊውን የራጉኤልን ልጅ ኦባብን፦ እግዚአብሔር፦ ለእናንተ እሰጠዋለሁ ወዳለው ስፍራ እንሄዳለን እግዚአብሔር ስለ እስራኤል መልካምን ነገር ተናግሮአልና አንተ ከእኛ ጋር ና፥ መልካምን እናደርግልሃለን አለው። እርሱም፦ አልሄድም፥ ነገር ግን ወደ አገሬና ወደ ዘመዶቼ እሄዳለሁ አለው። እርሱም፦ እባክህ፥ በምድረ በዳ የምንሰፍርበትን አንተ ታውቃለህና፥ እንደ ዓይኖቻችንም ትሆንልናለህና አትተወንከእኛም ጋር ብትሄድ እግዚአብሔር ከሚያደርግልን መልካም ነገር ሁሉ እኛ ለአንተ እናደርጋለን አለ።ከእግዚአብሔርም ተራራ የሦስት ቀን መንገድ ያህል ተጓዙ የእግዚአብሔርም የኪዳኑ ታቦት የሚያድርበትን ስፍራ ይፈልግላቸው ዘንድ የሦስት ቀን መንገድ ቀደማቸው።"(ዘኁ 10:29-33)
ታላቂቷ ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኖራለች!!!
ምንጭ፡-http://zeaddisu.blogspot.com/2013/01/blog-post.html
1 ከ እስራኤላውያን ውጪ ያለ ታላቅ ህዝብ ፡-ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያዊው ዝሪ አንድ ሚልዮን ሰራዊትና ሶስት መቶ ሰረገሎችን ይዞ ወደ እስራኤል ዘመተ በዚህም የተደናገጠው የእስራኤል ንጉስ ወደ ፈጣሪው ጽሎት አደረሰ ጸሎትም ሲያደርስ ኢትዮጵያውያኑን " ታላቅ ሕዝብ " በማለት ጠራቸው እንግሊዘኛው መጽሀፍ ቅዱስ ይሄንን ሲተርጉመው " The Great Ethiopians " The Great Nation " በማለት ነው፡፡
“ኢትዮጵያዊውም ዝሪ አንድ ሚሊዮን ሰዎችና ሦስት መቶ ሰረገሎች ይዞ ወጣባቸው ወደ መሪሳም መጣ። አሳም ሊጋጠመው ወጣ፥ በመሪሳም አጠገብ ባለው በጽፋታ ሸለቆ ውስጥ ተሰለፉ። አሳም። አቤቱ፥ በብዙም ሆነ በጥቂቱ ማዳን አይሳንህም አቤቱ አምላካችን ሆይ፥ በአንተ ታምነናልና፥ በስምህም በዚህ ታላቅ ሕዝብ ላይ መጥተናልና እርዳን አቤቱ፥ አምላካችን አንተ ነህ ሰውም አያሸንፍህ ብሎ ወደ አምላኩ ወደ እግዚአብሔር ጮኸ።" (2መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 14:9 -11)
ታላቅ ሕዝብ የሚለውን ያዙልኝ
2.የሙሴ በኢትዮጵያ ላይ መሾም
የአይሁድ ፣ የክርስትናና የታሪክ ሊቃውንት ደግሞ በሙሴና በኢትዮጵያ ጉዳይ የሚደንቅ ታሪክ አላቸው:: አይሁዶች "ሙሴ ኢትዮጵያ ሄዶ ኢትዮጵያን አርባ አመት ገዝቷል" ብለው ሲከራክሩ የክርስትናና የታሪክ ሰዎች ደግሞ " ኢትዮጵያ ላይ እግዚአብሔር ሊሾመው ነበር እንጂ የኢትዮጵያ ንጉስ አልነበረም " ይላሉ።
የክርስትና ሊቃውንት የሚጠቅሱት አንዱ መከራክርያ ይሄ ነው። ሙሴ ሲና ተራራ ላይ በቆየ ወቅት እስራኤል የጥጃ ጣኦት አቁመው ለጥጃው መስገድ ጀመሩ:: እግዚአብሔርም በዚህ በጣም ተቆጣ:: ሕዝቡንም ሊያጠፋው እንደወደደና ሙሴንም ለሌላ ታላቅ ሕዝብ መሪ እንደሚያደርገው ገለጸለት ። ይሔ ከእስራኤል ውጭ ያለ ሌላ ታላቅ ሕዝብ ማን ነበር?
“እግዚአብሔርም ሙሴን፦ ከግብፅ ምድር ያወጣኸው ሕዝብህ ኃጢአት ሠርተዋልና ሂድ፥ ውረድ። ካዘዝኋቸው መንገድ ፈጥነው ፈቀቅ አሉ ቀልጦ የተሠራ የጥጃ ምስል ለራሳቸው አደረጉ፥ ሰገዱለትም፥ ሠዉለትም። እስራኤል ሆይ፥ እነዚህ ከግብፅ ምድር ያወጡህ አማልክትህ ናቸው አሉ ፤ሲል ተናገረው እግዚአብሔርም ሙሴን፦ እኔ ይህን ሕዝብ አየሁት፥ እነሆም አንገተ ደንዳና ሕዝብ ነው።አሁንም ቍጣዬ እንዲቃጠልባቸው እንዳጠፋቸውም ተወኝ አንተንም ለታላቅ ሕዝብ አደርግሃለሁ አለው።” (ዘጸአት 32 ፡7-10)
ይሔ ከእስራኤል ጋር የሚወዳደር ሌላ ታላቅ ሕዝብ ማን እደሆነ ጻድቅ የነበረው የእስራኤል ንጉስ ቀድሞ ተናግሮታል(2መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 14:9):: በዘመነ ብሉይ የነበረው ነብዩ አሞጽም የተናገረው ይጠቀሳል ። "የእስራኤል ልጆች ሆይ፥ እናንተ ለእኔ እንደ ኢትዮጵያውያን ልጆቼ አይደላችሁምን?”(ትንቢተ አሞጽ 9፣7 )
ስለዚህ ሙሴ ሊሾምበት የነበረው ታላቅ ሕዝብ ኢትዮጵያ እንደነበረች ጥርጥር የለውም::
የሚደንቀው ግን የእስራኤላውያኑ እይታ ነው። የእስራኤላውያን የቀደሙ የታሪክ ሊቆቻቸውን ዜና መዋእል በመጥቀስ " ሙሴ ኢትዮጵያን አርባ አመት ገዝቷታል" ይሉናል። ይህንንም የጂውሽ ኢንሳይክሎፒዲያ (The Jewish Encyclopedia: A Descriptive Record of the History ..., Volume 9, page 48 edited by Isidore Singer, Cyrus Adle)ተጽፎ እናገኘዋለን፡፡
3. የመጀመርያዋ የእስራኤል ቀዳማዊ እመቤት የሙሴ ሚስት ኢትዮጵይዊቷ ሲፓራ ነበረች።
ኢትዮጵያን አትንኩ !!!
ከመጽሀፍ ቅዱስ እንደምንረዳው ሙሴ በምድር ሁሉ ካሉት ሰዎች " እጅግ ትሁት " እንደነበረና ( ዘኁ 12:3) በምድር ካሉ ሰዎች ሁሉ እግዚአብሔር አፍ ለአፍ እንደሚናገረውና የእግዚአብሔርንም መልክ ያየ ብቸኛው ጻድቅ እንደነበረ በሚገባ ተገልጿል።( ዘኁ 12:8) ታድያ ይህ ቀረህ የማይባለው ጻድቅና የሕግ መምህር ሙሴ መርጦ ያገባት ኢትዮጵያዊቱ ሲፓራን ነው።
በዚህም እስራኤላዊያኑ በማያገባቸው ነገር ገብተው ተናደዱ።ሊቀ ካህናቱ አሮንና ማርያም በይፋ ቁጣቸውን ገለጹ። ግን ምን ያደርጋል:: ሙሴ እንዴት ኢትዮጵያዊቷን ያገባል ብላ ያንጎራጎረችው ማርያም ስለዚህ ድፍረቷ በለምጽ ተቀጣች። ኢትዮጵያን አትንኩ !!!
"ሙሴም ኢትዮጵያይቱን አግብቶአልና ባገባት በኢትዮጵያይቱ ምክንያት ማርያምና አሮን በእርሱ ላይ ተናገሩ። እግዚአብሔርም ተቈጥቶባቸው ሄደ።ደመናውም ከድንኳኑ ተነሣ እነሆም፥ ማርያም ለምጻም ሆነች፥ እንደ አመዳይም ነጭ ሆነች አሮንም ማርያምን ተመለከተ፥ እነሆም፥ ለምጻም ሆና ነበር። አሮንም ሙሴን፦ ጌታዬ ሆይ፥ ስንፍና አድርገናልና፥ በድለንማልና እባክህ፥ ኃጢአት አታድርግብን።" (ኦሪት ዘኍልቍ 12: 1-12)
4. የኢትዮጵያዊቷ ሲፓራ ልጆች
ሙሴ ከኢትዮጵያዊት ሚስቱ ሁለት ልጆችን ወለደ:: እነዚህም ልጆች ስማቸው ጌርሳምና አልዓዛር ነበሩ::
“በዚያን ጊዜ የሙሴ አማት ዮቶር መልሶአት የነበረውን የሙሴን ሚስት ሲፓራን ሁለቱንም ልጆቿን ወሰደ።”(ዘጸ 18:2 )
እነዚህ ልጆች ሲያድጉ ባለስልጣን ሆነው ተሾሙ:: ቁጥራቸውም ታቦተ ጽዮንን ከሚያገለግሉት ከነገደ ሌዊ ሆነ::
"የእግዚአብሔርም ሰው የሙሴ ልጆች በሌዊ ነገድ ተቈጠሩ።የሙሴ ልጆች ጌርሳምና አልዓዛር ነበሩ።የሙሴ ልጅ የጌርሳም ልጅ ሱባኤል በቤተ መዛግብት ላይ ተሾሞ ነበር።"
ከነገደ ሴምና ከኢትዮጵያውያን ተወልደው በ እስራኤል ላይ ባለስልጣን የሆኑ የመጀመርያ ነጭና ጥቁሮች ( መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 23:14-16)
5. እስራኤልን ከግብጽ ወደ ኢየሩሳሌም እየመራ የወሰዳቸው ኢትዮጵያዊው ኦባብ
ሙሴ እስራኤልን ባሕር ከፍሎ ያሻገረ ታላቅ ነብይ ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ግን ሌላ የሚገርም ታሪክ ተጽፏል። ባሕረ ኤርትራን ከፍሎ ያሻገረው ታላቁ ነብይ ወደ ኢየሩሳሌም ሕዝቡን ይዞ የሚሄድበት መንገድ ጠፋው። ምንም እንኳን ቀን በአምደ ደመና ሌት ደግሞ በአምደ ብርሃን እየተመራ ሕዝቡን ይዞ ቢጓዝም ለሙሴ ሌላ ሰው መንገዱን ያሳያው ዘንድ ግድ ነበር። ይሄውም ሰው ኢትዮጵያዊው ኦባብ ራጉኤል ይባላል:: ሙሴ በራሱ አንደበት እንተ ለኛ ለእስራኤላውያን " አይኖቻችን ነህ " ብሎ የመሰከረለትና ሕዝበ እስራኤልን ይዞ ኢየሩሳሌም ያገባቸው ፣ ታቦተ ጽዮንንም ማደርያዋን ያዘጋጅ የነበረ ሃያል ኢትዮጵያዊ :: የኢትዮጵያዊቷ የሙሴ ሚስት ወንድም ኦባብ ወልደ ራጉኤል
"ሙሴም የሚስቱን አባት የምድያማዊውን የራጉኤልን ልጅ ኦባብን፦ እግዚአብሔር፦ ለእናንተ እሰጠዋለሁ ወዳለው ስፍራ እንሄዳለን እግዚአብሔር ስለ እስራኤል መልካምን ነገር ተናግሮአልና አንተ ከእኛ ጋር ና፥ መልካምን እናደርግልሃለን አለው። እርሱም፦ አልሄድም፥ ነገር ግን ወደ አገሬና ወደ ዘመዶቼ እሄዳለሁ አለው። እርሱም፦ እባክህ፥ በምድረ በዳ የምንሰፍርበትን አንተ ታውቃለህና፥ እንደ ዓይኖቻችንም ትሆንልናለህና አትተወንከእኛም ጋር ብትሄድ እግዚአብሔር ከሚያደርግልን መልካም ነገር ሁሉ እኛ ለአንተ እናደርጋለን አለ።ከእግዚአብሔርም ተራራ የሦስት ቀን መንገድ ያህል ተጓዙ የእግዚአብሔርም የኪዳኑ ታቦት የሚያድርበትን ስፍራ ይፈልግላቸው ዘንድ የሦስት ቀን መንገድ ቀደማቸው።"(ዘኁ 10:29-33)
ታላቂቷ ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኖራለች!!!
ምንጭ፡-http://zeaddisu.blogspot.com/2013/01/blog-post.html
Comments
Post a Comment